አዳዲስ ጥቅሶችን በቅርቡ በ Beamlack.wordpress.com ይጠብቁ

የመጀመሪያውን ጥቅስ እነሆኝ 1111111111111111

የመጨረሻው ዘመንና የክርስቶስ ዳግም ምፅዓት

የመጨረሻው ዘመን ፦ በመጽሐፍ ቅዱስ የዘመንና የነገሮች ጅማሬ እንዳለው ሁሉ የዘመንና የነገሮች ፍፃሜ ደግሞ እንዳለው ያስረዳናል። ስለዚህ በዘመን ፍፃሜ ሊሆኑ ስለተቃረቡ እውነቶች በዝርዝር መረዳቱ ከመሰረታዊ የክርስትና እምነታችን አንዱና ዋናው ነገር ስለሆነ ይህንን ማወቅ የማንኛውም አማኝ ግዴታና የቤተ ክርስቲያንም ሃላፊነት ነው። ስለመጨረሻው ዘመን ስንመለከት ልናተኩርባቸው የሚገቡ ዋና ዋና ነጥቦች እንደሚከተሉት ተገልፀዋል፦

1. ዳግም ምፅዓት

2. የቤተ ክርስቲያን መነጠቅ

3. የመምጣቱ ምልክቶች

4. ታላቁ የመከራ ዘመን

5. የሙታን ትንሳኤና የነጭዙፋን ፍርድ

6. የዘላለም ሕይወት

የጌታ ዳግም ምፅዓት ፦ የጌታን ዳግም ምፅዓት የሚጠባበቁትም ሆነ በመምጣቱ ተጠቃሚ የሚሆኑት ዳግም ተወልደው የእግዚአብሔር ቤተሰብ የሆኑቱ ብቻ ናቸው።

የምፅዓቱ ተጠቃሚዎች ከመጽሐፍ ቅዱስ አንፃር በጥቂቱ ስንመለከት፦

ሀ. በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉት ትንቢታዊ ቃሎች የሚረጋገጡበት ነው – ማቴ 24፡44-46፣ ሉቃ 21፡34-36፣ ሐዋ 1፡11

ለ. የክርስቲያኖች ተስፋ የሚጠናቀቅበት ነው ቲቶ 2፡13፣ ዮሐ 14፡1-5

ሐ. የክርስቲያኖች መጽናኛና የአለምን መከራ እንዲረሱ የሚያደርግ ነው – 1ተሰ 4፡14

ስለ ጌታ ዳግም ምፅዓት ስናስብ ሁለት መሰረታዊ ነገሮች አብረን ማሰብ ወይም ማወቅ አለብን። ይኸውም ጌታ ለቅዱሳን ይመጣል የሚለውን 1ተሰ 4፡16-17 እና ከቅዱሳን ጋር ይመጣል የሚለውን ነው – ሐዋ 1፡11፣ ራዕ 1፡7፣ ማቴ 24፡29-31። የጌታችን አመጣጡ በአካላዊና ለሁሉም ሊታይ በሚችል አይነት ይገለጣል።

የቤተ ክርስቲያን መነጠቅ ፦ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ ሙሽራ እንደሆነች የእግዚአብሔር ቃል ይመሰክራል – ራዕ 22፡17፣ 2ቆሮ 11፡1-2። ስለዚህ የእርሱ መገለጥ ለቤተ ክርስቲያን ታላቅ ደስታና የስራዋ መደምደሚያ ስለሆነ ለእርሷ የተለየ ጉዳይ ነው።

የመምጣቱ ምልክቶች ፦ የጌታ መምጣት ቀን ማንም እንደማያውቅ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያስረዳል – ማቴ 24፡36፣ ማር 13፡32። ለመምጣቱ ምልክቶች በግልጽ ተቀምተዋል። ታላቅ የወንጌል ስርጭት ይካሄዳል – ማቴ 24፡14፣ በምድር ላይ ችግር፣ መከራና መናወጥ ይሆናል – ማቴ 24፡3-14፣ 2ጢሞ 3፡1-5። እስራኤል በታሪክ ከብዙህ ሺህ አመት በኋላ በመንግስት ደረጃ ትዋቀራለች – ኢሳ 11፡12፣ ሉቃ 21፡29

ታላቁ የመከራ ዘመን ፦ ከክርስቶስ ዳግም መምጣት በፊት ወይም ከቅዱሳን ንጥቀት በኋላ ሰባት የመከራ ዘመናት በምድር ላይ ይሆናሉ። ቢሆንም ቤተ ክርስቲያን ስለተነጠቀች የዚህ መከራ ተካፋይ አትሆንም – ራዕ 3፡20። በዚህ ዘመን አይሁዳውያን በተለየ ሁኔታ መንግስታቸውን ከሃሰተኛ መሲህ ጋር በመሆን ያጠነክራሉ። ቃል ኪዳንም ያደርጋሉ – ኢሳ 11፡11፣ ዳን 9፡27። የፈረሰውን ቤተ መቅደስ በመስራት አምልኳቸውን ያደርጋሉ – ዳን 9፡24፣ ማቴ 24፡ 15-22። በመጨረሻው የመከራ ዘመን ጌታ ይታደጋቸዋል። በእርሱም ይሆናሉ ለዘላለም – ዘካ 8፡13-23 አሞፅ 9፡15 ሕዝ 34፡28። በመጨረሻው የመከራ ዘመን ሁለት ነገር ይሆናል። ጌታ ለሺህ አመት ከቅዱሳን ካር መንገሱ – ማቴ 24፡29-30 እና ሰይጣን ለሺህ አመት መታሰር ይሆናል – ራዕ 20፡3

የሙታን ትንሳኤና የነጭ ዙፋን ፍርድ ፦ ይህ የሙታን ትንሳኤ የሚሆነው ከአንድ ሺህ አመት የምድር ጌታ አገዛዝ ካበቃ በኋላ ነው። በዚህ በነጭ ዙፋን ላይ የተቀመጠው ጌታ ሲሆን በፊቱም የሚቆሙት በጌታ ሳያምኑ ሞተው የመጨረሻውን ፍርዳቸውን እንደስራቸው ለመቀበል ነው – ራዕ 20፡11-15። በጌታ ትንሳኤ መሃከል እና በቅዱሳን ትንሳኤ መሃከል እና በሙታን (በሃጢአተኞች) በሃከል አንድ ሺህ አመት ይኖራል። መጽሐፍ ቅዱስ ሰው አንድ ጊዜ ሞቶ ከዚያም በኋላ ስለሰራው ስራ የሚቀበለው ዋጋና ፍርድ እንደሚጠብቀው ያሳስበናል – ዕብ 9፡27።

የዘላለም ሕይወት ፦ በዘላለም ሕይወት ጅማሬ አሮጌው አልፎ አዲስ ነገር ይጀመራል።

ስለዚህ ክርስቲያን ማን ነው?

መልስ 1፦ ዌብስተር መዝገበ ቃላት ክርስቲያን ማለት “በክርስቶስ የሚያምን ወይንም በክርስቶስ ትምህርት በተመሠረተ ሃይማኖት የሚያምን ሰው” ነው ሲል ያስቀምጠዋል። የክርስቲያን ምንነት ለመረዳት ይህ የዌብስተር ፍች መነሻ ሊሆነን ይችላል፤ ነገር ግን ልክ እንደሌሎቹ ዓለማዊ የሆኑ ፍችዎች ክርስቲያን መሆን የሚያመለክተውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነት ማስተላለፍ አይችልም።

ክርስቲያን የሚለው ቃል በሐዲስ ኪዳን ሦስት ጊዜ ተጠቅሶ እናገኝዋለን (የሐዋርያት ሥራ ፲፩፥፳፮፤ የሐዋርያት ሥራ ፳፮፥፳፰፤ ፩ኛ ጴጥሮስ ፬፥፲፮)። የኢየሱስ ተከታዮች ክርስቲያን የሚል ስም በመጀመሪያ በአንጾኪያ ተሰጣቸው (የሐዋሪያት ሥራ ፲፩፥፳፮)፤ ይህም ስም የተሰጣቸው ሥራቸውና ጸባያቸው እንደክርስቶስ ስለነበር ነው። በመጀመሪያ ይህ ስም ያልዳኑት የአነጾኪያ ሰዎች ክርስቲያን የሆኑትን ላይ ለማላገጥ ያወጡላቸው ስም ነበር። ቀትተኛ ተርጉሙም፣ “የክርስቶስ ማኀበር አባል” ወይንም “የክርስቶስ ተከታይ” ማለት ነው።

ቢሆንም ከጊዜ በኋላ “ክርስቲያን” የሚለው ቃል ትክክለኛ ትርጉሙ አጥቶ የክርስቶስ ተከታይ ለሆነው ሳይሆን ግብረ ገባዊ በሆነ መንገድ ለሚመላለስ ማንኛውንም ሃይማኖተኛ የሚሰጥ ስም ሆኖ እናገኘዋለን። ብዙ ሰዎች በ ኢየሱስ ክርስቶስ ባያምኑም አንኳን ወደ ቤተ ክርስቲያን በመመላለሳቸው ወይንም “ክርስቲያን” በሆነ አገር በመኖራቸው ብቻ ራሳቸውን ክርስቲያን ብለው ይሰይማሉ። ቢሆንም ግን ወደ ቤተ ክርስቲያን መመላለስ፣ ካነተ በታች የሆኑትን መርዳትና ጥሩ ሰው ሆኖ መገኘት ብቻ በራሱ ክርስቲያን አያደርግህም። አንድ ሰባኪ እንዳለው፣ “ወደ ቤተ ክርስቲያን መመላለስ አንድን ሰው ክርስቲያን አያደርገውም፤ ልክ ወደ ጋራዥ መመላለስ አንድን ሰው መኪና እንደማያደርገው ሁሉ።” የቤተ ክርስቲያን አባል መሆን፣ ጉባኤ መከታተልና የቤተ ክርስቲያንን ሥራ መሥራት ብቻ ክርስቲያን አያደርግህም።

መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስተምረን የምንሠራው በጎ ሥራ ብቻውን በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነትን አያስገኝልንም። ቲቶ ፫፥፭ እነዲህ ይለናል፤ “ስላደረግነው የጽድቅ ሥራ ሳይሆን፣ ከምሕረቱ የተነሣ አዳነን። ያዳነንም ዳግም ልደት በሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ መታደስ ነው።” ስለዚህ፣ ክርስቲያን ማለት በእግዚአብሔር እንደገና የተወለደና (ዮሐንስ ፫፥፫፤ ዮሐንስ ፫፥፯፤ ፩ኛ ጴጥሮስ ፩፥ ፳፫) እምነቱንም በክርስቶስ ያደረገ ሰው ነው። ኤፌሶን ፪፥፰ እነደሚለን፣ “በእምነት፣ በጸጋ ድናችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከ እናንተ አይደለም።” እውነተኛው ክርስቲያን ለኀጢአቱ ንስሓ የገባና በኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ያመነ ነው። እውነተኛ ክርስቲያኖች እምነታቸው ሃይማኖትን፣ ግብረ ገባዊ ሕጎችንና “አድርግ አታድርግ” ዝርዝሮችን ላይ አይደለም።

እውነተኛ ክርስቲያን እምነቱ በክርስቶስ ያደረገ፣ ክርስቶስ መስቀል ላይ የሞተው ለኀጢአታችን ሲል እነደሆነና በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተነስቶ ሞት ላይ አቸናፊነቱን ያረጋገጠው በሱ ለሚያምኑ ዘለዓለማዊ ሕይወትን ለመስጠት መሆኑን ያመነ ማለት ነው። ዮሐንስ ፩፥፲፪ እንዲህ ይለናል፤ “ለተቀበሉትና በስሙ ላመኑት ሁሉ ግን የእግዚአብሔር ልጆች የመሆን መብት ተሰጣቸው።” እውነተኛው ክርስቲያን የእግዚአብሔር ልጅ ነው፤ እንዲሁም የእግዚአብሔር ቤተሰብ አባልና በክርሰቶስ አዲስ ሕይወት የተሰጠው ነው። የእውነተኛ ክርስቲያን መለያ ለሌሎች በሚያሳየው ፍቅርና ለእግዚአብሔር ቃል በሚያሳየው መታዘዝ ነው (፩ኛ ዮሐንስ ፪፥፬፤ ፩ኛ ዮሐንስ ፪፥፲)።

በኢየሱስ ካመንኩ በኋላ የሚቀጥለው ርምጃ ምንድንው?

እነኳን ደስ ያለህ! ሕይወትን የሚቀይር ውሳኔ ነው የወሰንከው! “ቀጥሎስ?” ብለህ እየጠየቅክ ሊሆን ይችላል። “ከእግዚአብሔር ጋር ጉዞዬን እንዴት እጀምራለሁ?” የሚል ጥያቄ ሊኖርህ ይችላል። ከዚህ በታች የተጠቀሱት አምስት መመሪያዎች ከመጽሐፍ ቅዱስ ፊና ይሰጡሃል።

፩. ድነት ምን ማለት እነደሆነ በደንብ መረዳትህን አረጋግጥ።

፩ኛ ዮሐንስ ፭፥፲፫ እነደሚለን፣ “በእግዚአብሔር ልጅ ስም የምታምኑ እናንተ፣ የዘለዓለም ሕይወት እንዳላችሁ ታውቁ ዘንድ ይህን እጽፍላችኋለሁ።” እግዚአብሔር ድነትን በደንብ እነዲገባን ይፈልጋል። ድነት እነዳለን ጽኑ እምነት እንዲኖረን እግዚአብሔር ይሻል። ባጭሩ፣ የድነት ቁልፍ ነጥቦች እነዚህ ናቸው፤

(ሀ) ሁላችንም ኀጥአን ነን። እግዚአብሔርን የሚያስቀይም ሥራም ሠርተናል (ሮሜ ፫፥ ፳፫)።

(ለ) ለኀጢአታችንም ከእግዚአብሔር ጋር ለዘለዓለሙ መለያየት በተገባን ነበር (ሮሜ ፮፥፳፫)።

(ሐ) ኢየሱስ የኀጢአታችንን ዋጋ ለመቀበል መስቀል ላይ ሞተልን (ሮሜ ፭፥፰፤ ፪ኛ ቆሮንቶስ ፭፥፳፩)።

ይህ ነው እንግዲህ የድነት መልእክት! ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኜ ነው ብለህ ካመንክ ትድናለህ! ኀጢአትህ ሁሉ እነደተሰርየልህና እግዚአብሔርም እነደማይርቅህ ቃል ገብቶልሃል (ሮሜ ፰፥፴፰-፴፱፤ ማቴዎስ ፳፰፥፳)። ድነትህ የተረጋገጠው በክርሰቶስ መሆኑ አትርሳ (ዮሐንስ ፲፥፳፰-፳፱)። በኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት ካመንክ፣ የዘለዓለም ሕይወትህ በሰማይ ከእግዚአብሔር ጋር ይሆናል!

፪. መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስተምር ጥሩ ቤተ ክርስትያን ፈልግ።

ስለ ቤተ ክርስቲያን ስታስብ ሕንጻውን አይደለም። ቤተ ክርስቲያን ሕዝቡ ነው። የኢየሱስ አማኞች እርስ በራሳቸው ወገነኝነት እንዲኖራቸው ያስፈልጋል። ኢየሱስን ስለተቀበልክ፣ በምትኖርበት አጠገብ የሚገኝ በመጽሐፍ ቅዱስ የሚያምን ቤተ ክርስቲያን ፈልገህ ቄሱን አነጋግር። በኢየሱስ ክርስቶስ ስላለህ እምነት አማክረው።

የቤተ ክርስቲያን ሁለተኛው ጥቅም መጽሐፍ ቅዱስ ለማስተማር ነው። የእግዚአብሔር መመሪያዎች ሕይወትህ ላይ እንዴት መተገበር እንደምትችል ትማራለህ። ጠንካራና የተሳካ ክርስቲያናዊ ኑሮ ለመምራት መጽሐፍ ቅዱስን መረዳት ቁልፍ ነው። ፪ኛ ጢሞቴዎስ ፫፥፲፮-፲፯ እንደሚለን፣ “ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለባቸው ናቸው፤ ለማስተማር፣ ለመገሠጽ፣ ለማቅናት በጽድቅም መንገድ ለመምከር ይጠቅማሉ፤ ይኸውም የእግዚአብሔር ሰው ለመልካም ሥራ ሁሉ ብቁ ሆኖ እንዲገኝ ነው።”

ሶስተኛው የቤተ ክርስቲያን ጥቅም ደግሞ ለአምልኮ ነው። አምልኮ ደግሞ ላደረገልን ሁሉ ለእግዚአብሔር ምስጋና ማድረስ ማለት ነው። እግዚአብሔር አድኖናል። እግዚአብሔር ይወደናል። እግዚአብሔር ያስብልናል። እግዚአብሔር መንገድ ይመራናል። ለዚህ ሁሉ ታድያ እነዴት አናመስግነው? እግዚአብሔር ቅዱስ፣ ጻድቅ፣ ሩሩና ጸጋ የተሞላ ነው። ራእይ ፬፥፲፩ እንዲህ ያውጃል፣ “ጌታችንና አምላካችን ሆይ፤ ክብርና ሞገስ፣ ኀይልም ልትቀበል ይገባሃል፤ አንተ ሁሉን ፈጥረሃልና፤ በፈቃድህም ተፈጥረዋልና፤ ሆነዋልምና።”

፫. ወደ እግዚአብሔር ትኩረት የምትሰጥበት በቀን የተወሰነ ጊዜ ይኑረህ።

በየቀኑ የተወሰነ ሰዓት ለእግዚአብሔር ትኩረት መስጠት አለብን። አንዳንድ ሰዎች ይህንን “የጸጥታ ሰዓት” ይሉታል። ሌሎቹ ደግሞ “ትጋት” ይሉታል፣ ራሳቸውን ለእግዚአብሔር በትጋት አተኩሮ መስጠታቸውን ለማስመልከት። ይህንን የአተኩሮ ጊዜ፣ አንዳንዶች ጠዋት ይመርጣሉ፤ ሌሎች ደግሞ ከቀትር በኋላ። ይህንን ሰዓት ምን ስም ብንሰጠውም ሆነ በየተኛው የቀን ክፍለ ጊዜ ብናረገውም ወሳኝነት የለውም። ወሳኝ ሁኔታው ግን ከእግዚአብሔር ጋር የግል ሰዓት መለየታችን ነው። ይህ የግል ጊዜያችን ምን እናከናውንበታለን?

(ሀ) ጸሎት። ጸሎት ከእግዚአብሔር ጋር ንግግር ነው። ጭንቀትህም ሆነ ችግርህ ለእግዚአብሔር ንገረው። ጥበብና አመራር እንዲለግሥህ እግዚአብሔርን ጠይቀው። ፍላጎትህን እንዲያሟላልህ እግዚአብሔርን ጠይቀው። ምን ያህል እነደምታፈቅረውና እንደምታመሰግነው ንገረው። ጸሎት እንግዲህ ይህ ነው።

(ለ) የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ። በቤተ ክርስቲያን ወይንም በሰንበት ትምርህት ቤት ከምትማረው ውጪ፣ መጽሐፍ ቅዱስ በግልህ ማንበብ አለብህ። ስኬታማ ክርስቲያናዊ ሕይወት ለመምራት የሚያሰፈልጉህ ሁሉ መጽሐፍ ቅዱስ በውስጡ ይዟል። ብልህ ውሳኔዎችን ለመወሰን፣ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለማወቅ፣ ሌሎቹንን በደንብ ለማስተማርና በመንፈስ ለመበልጸግ የሚረዱንን የእግዚአብሔር መመሪያዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይገኛሉ። መጽሐፍ ቅዱስ ለኛ የእግዚአብሔር ቃል ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ሕይወታችንን እግዚአብሔርን ደስ በሚያሰኝና በሚያረካ መንገድ እንዴት መምራት እንዳለብን የሚያሳየን ከእግዚአብሔር የተሰጠን መምሪያ መጽሐፍ ነው።

(፬) በመንፈስ ሊያበረቱህ ከሚችሉ ሰዎች ጋር ግንኙነት አጠንክር።

፩ኛ ቆሮንቶስ ፲፭፥፴፫ እንደሚለን፣ “አትሳቱ፤ ‘መጥፎ ጓደኝነት መልካሙን ጠባይ ያበላሻል።”’ መጽሐፍ ቅዱስ “መጥፎ” ሰዎች ተጽዕኖ እንዳያሳድሩብን ያስጠነቅቀናል። ከእነዚህ አይነቶቹ ጋር መዋል በቀላሉ ሐጢአት ለመሥራት መገፋፋት ይሆናል፤ ምክኒያቱም ሲውል ሲያድር እነርሱን መምሰላችን አይቀርምና። ለዚህም ነው በእግዚአብሔር መንገድ ከሚመላለሱት ሰዎች ጋር ብቻ መዋል ያለብን።

ሊያበረታቱህ የሚችሉ አንድ ሁለት ሰዎች ከጉባኤህ ፈልግ (ዕብራውያን ፫፥፲፫፤ ፲፥፳፬)። ጓደኞችህን የጸጥታ ጊዜህን፣ የቀን ተቀን ተግባራትህንና ከእግዚአብሔር ጋር ለምታደርገው ጉዞህን እንዲከታተሉልህ ጠይቃቸው። አንተም በተራህ ይህንኑ እንድታደርግላቸው ጠይቃቸው። ከጓደኞችህ ጋር የምትካፈላቸውን አጋጣሚዎች እግዚአብሔር እንዲፈጥርልህ ጠይቀው።

፭. ተጠመቅ።

ጥምቀትን አስመልክቶ ብዙዎች የተሳሳተ አመለካከት አላቸው። “መጠመቅ” የሚለው ቃል ውኃ ውስጥ መነከርን ያመለክታል። ጥምቀት መጽሐፍ ቅዱሳዊ በሆነ መንገድ አዲሱ እምነትህን ለክርስቶስ ማወጅህንና ለሱ ራስህን ማስገዛትህን ያሳያል። ውኃ ውስጥ መነከር ከክርስቶስ ጋር መቀበርን ያመለክታል። ተነክረህ መውጣትህ ደግሞ የክርስቶስ ከሙታን መነሳትን ያመለክታል። ስለዚህም፣ መጠመቅ ከክርስቶስ መሞት፣ መቀበርና ከሙታን መነሳት ጋር መካፈልህን ያሳያል።

ጥምቀት አይደለም የሚያድንህ። ጥምቀት ከኀጢአትህ አያነጻህም። ጥምቀት በመሠረቱ በክርስቶስ ማመንህንና ለሱ መገዛትህን በአደባባይ የምታውጅበት ነው። ለመጠመቅ ዝግጁ ከሆንክ ቄስህን ወይም ፓስተርህን  አነጋግር።


ክርስትና ምንድ ነው? ክርስቲያኖች በምን ያምናሉ?

ጥያቄ 1፦ክርስትና ምንድ ነው? ክርስቲያኖች በምን ያምናሉ?

መልስ 1፦ 1ኛ ቆሮንቶስ 15፡1-4 እንዲህ ይላል “ወንድሞች ሆይ፣ የሰበክሁላችሁን ደግሞም የተቀበላችሁትን በእርሱም ደግሞ የቆማችሁበትን፣ በእርሱም ደግሞ የምትድኑበትን ወንጌል አሳስባችኋለሁ፣ በከንቱ ካላመናችሁ በቀር፣ ብታስቡት፥ በምን ቃል እንደ ሰበክሁላችሁ አሳስባችኋለሁ። እኔ ደግሞ የተቀበልኩትን ከሁሉ በፊት አሳልፌ ሰጠኋችሁ። እንዲህ ብዬ፦ መፅሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለኃጢያታችን ሞተ፣ ተቀበረም፤ መፅሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሳ።”

በአጭሩ የክርስትና እምነት መሰረት ይህ ነው። ከሌሎች እምነቶች በተለየ መልኩ ከሐይማኖታዊ ልምምድ ይልቅ ክርስትና የሚያተኩረው በግንኙነት ላይ ነው። ይህን “አድርግና አታድርግ” የሚል መመሪያ ከመዘርዘር ይልቅ የክርስቲያን ግብ ከእግዚሐብሔር አባት ጋር የቀረበ ግንኙነት እንዲኖር ያበረታታል። ያ ግንኙነት እውን ሊሆን የቻለው በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራና መንፈስ ቅዱስ በክርስቲያኑ ሕይወት በሚኖረው አገልግሎት ነው።

መፅሐፍ ቅዱስ የእግዚሐብሔር መንፈስ ያለበትና ስህተት የሌለበት፣ ትምህርቱም የመጨረሻ ስልጣን ያለው መሆኑን ክርስቲያኖች ያምናሉ። (2ኛ ጢሞቲዎስ 3፡ 16፣ 2ኛ ጴጥሮስ 1፡ 20-21)። ክርስቲያኖች በሦስት አካላት በሚኖር በአንድ እግዚሐብሔር ያምናሉ። ይኸውም በአብ፣ በወልድ(በኢየሱስ ክርስቶስ) እና በመንፈስ ቅዱስ ነው።

የሰው ልጅ የተፈጠረው በተለይ ከእግዚሐብሔር ጋር ግንኙነት ለማድረግ እንደሆነ ክርስቲያኖች ያምናሉ። ነገር ግን ኃጢአት ሁሉንም ሰዎች ከእግዚሐብሔር አለያይቶአቸዋል። (ሮሜ 3፡ 23፣ 5፡ 12)። ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም ሲመላለስ ፍፁም አምላክ፣ ፍፁም ሰው ሆኖ እንደኖረና በመስቀል ላይ እንደሞተ ክርስቲያኖች ያምናሉ።( ፊሊጲስዩስ 26፡ 6-11)። በመስቀል ላይ ከሞተ በኋላ ክርስቶስ ተቀብሮ እንደገና በመነሳት አሁን በአባቱ ቀኝ ሆኖ ለአማኞች ለዘላለም እንደሚማልድ ክርስቲያኖች ያምናሉ።(ዕብራውያን 7፡ 25)። የኢየሱስ በመስቀል ላይ መሞት ሁሉም ሰዎች በኃጢያት ምክንያት የነበረባቸውን ዕዳ ለመክፈል ብቁ እንደሆነ ክርስትና ያምናል። ይህ ነው እንግዲህ በእግዚሐብሔርና በሰው መካከል ተቋርጦ የነበረውን ግንኙነት እንዲታደስ ያደረገው ነገር።( ዕብራውያን 9፡ 11-14፣ 10፡ 10፣ ሮሜ 5፡8፣ 6፡ 23)።

አንድ ሰው ለመዳን ከፈለገ በመስቀሉ ላይ በተፈፀመው የክርስቶስ ሥራ እምነቱን ማኖር አለበት። ማንም ሰው ክርስቶስ በእርሱ ፋንታ እንደሞተና ለራሱ ኃጢያት ዋጋ እንደከፈለለት እንደገናም እንደተነሳ ካመነ፣ ያ ሰው ድነት አግኝቷል ማለት ነው። ማንም ሰው ድነትን ለማግኘት ምንም ማድረግ አይችልም። ማንም ግለሰብ በራሱ ወይም በራስዋ “መልካም በማድረግ” እግዚሐብሔርን ደስ ሊያሰኙት አይችሉም። ምክንያቱም ሁላችንም ኃጢያተኞች ስለሆን። (ኢሳያስ 53፡ 6፣ 64፡ 6-7)። ሁለተኛም ከዚህ የበለጠ የሚሰራ ሥራ የለም። ምክንያቱም ክርስቶስ ሁሉን ሥራ አከናውኖታል! በመስቀል ላይ ሆኖ ክርስቶስ እንዲህ ብሏል “ተፈፀመ” (ዮሐንስ 19፡ 30)።

ድነትን ለማግኘት ማንም ምንም ማድረግ እንደሌለበት ሁሉ እርሱ/እርሷ ክርስቶስ በመስቀል ላይ በሰራው ሥራ ከታመኑ በሌላው በኩል ደግሞ እርሱ/እርሷ ድነታቸውን ለማጣት ምንም ማድረግ የለባቸውም። ምክንያቱም ሥራው ተሰርቶ ያለቀው በክርስቶስ በመሆኑ! ድነት በምንም መንገድ በተቀባዩ ላይ የተመሰረተ አይደለም። ዮሐንስ 10፡ 27-29 እንዲህ ይላል “በጎቼ ድምፄን ይሰማሉ፣ እኔም አውቃቸዋለሁ፣ ይከተሉኝማል፣ እኔም የዘላለም ሕይወት እሰጣቸዋለሁ፣ ለዘላለምም አይጠፉም፣ ከእጄም ማንም አይነጥቃቸውም። የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል፣ ከአባቴም እጅ ሊነጥቃቸው ማንም አይችልም።”

አንዳንዶች እንዲህ ሊያስቡ ይችላሉ። “ይህ ትልቅ ነገር ነው- አንዴ ድነትን ካገኘሁ ያሻኝን እያደረግሁ ድነቴን ላጣ አልችልም!” ድነት ግን ነፃ ሆኖ የፈለጉትን ማድረግ ማለት አይደለም። ድነት ማለት የድሮውን የኃጢያት ተፈጥሮ ከማገልገል ነፃ በመሆን ከእግዚሐብሔር ጋር ያለውን ግንኙነት ለማራመድ ነፃ መውጣትን ነው የሚያሳየው። ከዚህ ቀደም ለኃጠያት ባርያዎች ነበርን፤ አሁን ግን እኛ የክርስቶስ ባርያዎች ነን። (ሮሜ 6፡ 15-22)። አማኞች በዚህ ዓለም ላይ ከኃጢያተኛው ተፈጥሮአቸው ጋር እስካሉ ድረስ፣ ከኃጢያት ጋር የማያቋርጥ ትግል እንደሚያደርጉ የታወቀ ነው። ይሁን እንጂ ከኃጢያት ጋር በሚያደርጉት ትግል ክርስቲያኖች ድል ሊቀዳጁ የሚችሉበት መንገድ አለ። የእግዚሐብሔር ቃል (መፅሐፍ ቅዱስ) በማጥናትና በሕይወታቸው በመተግበር፣ ራሳቸውን በመንፈስ ቅዱስ ሥር በማዋል፣ የእግዚሐብሔርን ቃል በመታዘዝ፣ የዕለት ተዕለት ኑሮአቸው በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እንዲመራ መፍቀድ ይጠበቅባቸዋል። ስለዚህ በርካታ የእምነት ሥርዓቶች የተወሰኑ ነገሮችን እንዲያደርጉ ወይም እንዳያደርጉ ግዴታ ሲጥሉ፣ ክርስትና ግን የእኛን የኃጢያት ዋጋ ለመክፈል ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሞቶ እንደገና እንደተነሳ ማመን ብቻ ነው የሚጠይቀው። ያንተ የኃጢያት ዕዳ ተከፍሏል። ስለዚህ ከእግዚሐብሔር ጋር ሕብረት ማድረግ ትችላለህ። በኃጢያተኛው ተፈጥሮህ ላይ ድል በመቀዳጀት፣ ለእግዚሐብሔር በመታዘዝ፣ ከእርሱ ጋር በሕብረት ለመራመድ መንገድ ተከፍቶልሐል። ይህ ነው እንግዲህ እውነተኛው መፅሐፍ ቅዱሳዊ ክርስትና ማለት።

ክርስትና

“Christian practices are not activities we do to make something spiritual happen in
our lives. Nor are they duties we undertake to be obedient to God. Rather, they are
patterns of communal action that create openings in our lives where the grace, mercy,
and presence of God may be made known to us. They are places where the power of
God is experienced. In the end, these are not ultimately our practices but forms of
participation in the practice of God.”

Christian practices are things Christian people do together over time to address fundamental human needs in the light of and in response to God’s grace to all creation through Christ Jesus

When we live the practices of Christian faith, we join together with one another, with Jesus, and with the communion of saints across time and space in a way of life that resists death in all its forms – a way of life that is spilling over with the Life of God for creation, for our neighbors, and for ourselves.

Why Practices Matter???
How does this idea of “practices” help us think about — and live — the Christian life?

Practices point beyond the individualism of the dominant culture to disclose the social (i.e., shared) quality of our lives, and especially the social quality of Christian life, theology, and spirituality. Our thinking and living take place in relation to God and also to one another, to others around the world and across the centuries, and to a vast communion of saints. In this regard, Practicing Our Faith is not a self-help book but a mutual-help book.

Practices help us to understand our continuity with the Christian tradition — an important matter during this time of change and in the midst of a culture infatuated with what is new. The way of life we are describing is historically rooted, and the history from which Christian practices emerge is an expansive one that encompasses many cultures and denominational traditions. In the terms used here, “practices” endure over time and across cultures; what changes are the specific moves by which specific groups of Christians embody these practices in different times and places. Attention to practices, in this sense, can help contemporary people to treasure their continuity with the past, even while also helping them to embrace the future with hope and creativity, as members of a living tradition.

All of this means that people need to craft the specific forms each practice can take within their own social and historical circumstances. This approach thus requires attention to the concrete and down-to-earth quality of the Christian life. It invites attention to details such as gestures and the role of material things.

Practices make us think about who we truly are as the created and newly created children of God. An important claim is that Christian practices address “fundamental human needs.” We live in a culture that is very confused about what people need — a culture where a plethora of dubious “needs” are constantly being constructed and marketed. In contrast, awareness of Christian practices helps us to reflect theologically on who people really are and what we really need.

A practice is small enough that it can be identified and discussed as one element within an entire way of life. But a practice is also big enough to appear in many different spheres of life. For example, the Christian practice of hospitality has dimensions that emerge as (1) a matter of public policy; (2) something you do at home with friends, family, and guests; (3) a radical path of discipleship; (4) part of the liturgy; (5) a movement of the innermost self toward or away from others; (6) a theme in Christian theology; and probably much else. Thinking about this one practice can help us make connections across spheres of life-connections that often get disrupted in our fragmented society. For example, reflection on the Christian practice of hospitality would provide a way of exploring the relations between spirituality and social justice.

All people engage in most or all of the practices in Practicing Our Faith in one way or another. After all, all human beings necessarily rest, encounter strangers, rely on one another’s help when ill, and so on. However, those who embrace Christian practices engage in these fundamental human activities in the light of God’s presence and in response to God’s grace is it is known in Jesus Christ. Ultimately, Christian practices can be understood not as tasks but as gifts. Within these practices, we do not aim to achieve mastery (e.g., over time, strangers, death, nature) but rather to cultivate openness and responsiveness to others, to the created world, and to God.

Christian practices add up to a way of life. They are woven together: if one is missing, all are distorted in some way. On the other hand, because they are woven together, any one practice can become a gateway into the whole way of life.

Practices heal the division between thinking and doing (which many modern people have thought are separate) and show how much each is related to the other. On the one hand, practices are forms of doing: A child or adult can participate in a practice such as hospitality through warm acts of welcome, even without comprehending the biblical stories and theological convictions that encourage and undergird this practice. Most of our practicing takes place at this unreflective level, as we go about our daily living. At the same time, practices are not only behaviors. They are meaning-full. Within a practice, thinking and doing are inextricably knit together. Those who offer hospitality come to know themselves, others, and God in a different way, and they develop virtues and dispositions that are consistent with this practice. When people participate in a practice, they are embodying a specific kind of wisdom about what it means to be a human being under God, even if they could not readily articulate this wisdom in words.

While affirming the unreflective character of most participation in practices, it is also helpful to reflect in the light of our faith on the shape and character of the practices that make up our way of life. Indeed, such reflection may be especially important at this point in history, when the shape of our lives is changing so rapidly. These are practices in which Christian communities have engaged over the years and across many cultures, practices which it is now our responsibility to receive and reshape in lively ways in our own time and place. When we do reflect on practices such as those explored in Practicing Our Faith, we can see that central themes of Christian theology are integrally related to each Christian practice: our practices are shaped by our beliefs, and our beliefs arise from and take on meaning within our practices. For example, Stephanie Paulsell bases her chapter and book on Honoring the Body on the theological convictions that God created human bodies and declared that they are good; that God shared our physical condition in the incarnation of Jesus; and that God overcame death through Jesus’ resurrection. Through everyday activities — for example, resting, bathing, and caring for those who suffer — we live out our deepest convictions about who we are as embodied children of God in specific, often stumbling, ways. We learn to do so from those with whom we share our lives, and likewise, it is with them that we need to reflect on practices as they take shape in the light of and in response to God’s grace.